በፓኪስታን ኢስላማባድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በይፋ ተመረቀ

6 Mons Ago
በፓኪስታን ኢስላማባድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በይፋ ተመረቀ

በፓኪስታን ኢስላማባድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በይፋ መመረቁን የኢ.ፌ.ደ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያጠናከሩ የመጡት ኢትዮጵያ እና ፓኪስታን አዳዲስ የግንኙነት ምዕራፎችን እየከፈቱ ይገኛሉ።

ከቀናት በፊት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቀጥታ በረራ ከአዲስ አበባ ወደ ካራቺ የጀመረ ሲሆን በዛሬው ዕለትም በኢስላማባድ ከአንድ ዓመት በፊት የተከፈተው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዛሬ በይፋ ተመርቋል።

ኤምባሲውን መርቀው የከፈቱት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ እና የፓኪስታን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ ሂና ራቢኒ ካሃን ናቸው።