የሀረሪ ክልል ምክር ቤት የቀረበለትን የካቢኔ አባላት ሹመት አጸደቀ

7 Mons Ago 1147
የሀረሪ ክልል ምክር ቤት የቀረበለትን የካቢኔ አባላት ሹመት አጸደቀ

የሀረሪ ክልል ምክር ቤት የቀረበለትን የካቢኔ አባላት ሹመት ተቀብሎ አጽድቋል።

የካቢኔ አባላት ሹመት በምክር ቤቱ የጸደቀው በክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ አቅራቢነት ነው።

በዚህ መሰረትም ፡-

1ኛ ወ/ሮ ሮዛ ኡመር - የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ልማት ቢሮ ኃላፊ

2ኛ ወ/ሮ ኢክራም አብዱልቃድር - የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ

3ኛ አቶ አሰፋ ቶልቻ- የሀረር ከተማ ማዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጅ

4ኛ አቶ ኡስማኤል ዩሱፍ- የክልሉ ኢንተርፕራይዞች ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ

5ኛ ወ/ሮ ረምዚያ አብዱልወሃብ- የክልሉ ሴቶች፣ ሕጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ

6ኛ አቶ ቶፊቅ መሀመድ- የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ

7ኛ አቶ መሀመድ ያህያ- የክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ኃላፊ

8ኛ አቶ ያሲን አብዱላሂ- የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ

9ኛ ወ/ሮ ደሊላ ዩሱፍ- የክልሉ ሲቪል ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ

10ኛ አቶ አብዱማሊክ በከር- የክልሉ ዋና ኦዲተር

በተጨማሪም በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ አቅራቢነት በተጓደሉት የክልሉ ብዙሃን መገናኛ ኤጀንሲ ቦርድ ሰብሳቢ እና አባላትን ሰይሟል

በዚሁ መሰረት

1ኛ አቶ ጌቱ ወዬሳ- የክልሉ የብዙሃን መገናኝ ኣጀንሲ ቦርድ ሰብሳቢ

2ኛ አቶ መሀመድ ያህያ- የክልሉ የብዙሃን መገናኝ ኣጀንሲ ቦርድ አባል

3ኛ አቶ ቶፊቅ መሀመድ-የክልሉ የብዙሃን መገናኝ ኣጀንሲ ቦርድ አባል እንዲሆኑ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።

በክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ አሪፍ መሀመድ አቅራቢነት

1ኛ አቶ ጅብሪል መሀመድ- የክልሉ ምክር ቤት የኢኮኖሚ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ

2ኛ ወ/ሮ ፊቲያ ሳኒ - በክልሉ ምክር ቤት የበጀትና ፋይናንስ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሰቢ ሆነው እንዲያገለግሉ ምክር ቤቱ በሙሉ ድምፅ ማፅደቁን የክልሉ ከሙዩኒኬሽን ቢሮ መረጃ አመልክቷል።


አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top