የሀረሪ ክልል ምክር ቤት የቀረበለትን የካቢኔ አባላት ሹመት አጸደቀ

155 Days Ago
የሀረሪ ክልል ምክር ቤት የቀረበለትን የካቢኔ አባላት ሹመት አጸደቀ

የሀረሪ ክልል ምክር ቤት የቀረበለትን የካቢኔ አባላት ሹመት ተቀብሎ አጽድቋል።

የካቢኔ አባላት ሹመት በምክር ቤቱ የጸደቀው በክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ አቅራቢነት ነው።

በዚህ መሰረትም ፡-

1ኛ ወ/ሮ ሮዛ ኡመር - የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ልማት ቢሮ ኃላፊ

2ኛ ወ/ሮ ኢክራም አብዱልቃድር - የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ

3ኛ አቶ አሰፋ ቶልቻ- የሀረር ከተማ ማዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጅ

4ኛ አቶ ኡስማኤል ዩሱፍ- የክልሉ ኢንተርፕራይዞች ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ

5ኛ ወ/ሮ ረምዚያ አብዱልወሃብ- የክልሉ ሴቶች፣ ሕጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ

6ኛ አቶ ቶፊቅ መሀመድ- የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ

7ኛ አቶ መሀመድ ያህያ- የክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ኃላፊ

8ኛ አቶ ያሲን አብዱላሂ- የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ

9ኛ ወ/ሮ ደሊላ ዩሱፍ- የክልሉ ሲቪል ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ

10ኛ አቶ አብዱማሊክ በከር- የክልሉ ዋና ኦዲተር

በተጨማሪም በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ አቅራቢነት በተጓደሉት የክልሉ ብዙሃን መገናኛ ኤጀንሲ ቦርድ ሰብሳቢ እና አባላትን ሰይሟል

በዚሁ መሰረት

1ኛ አቶ ጌቱ ወዬሳ- የክልሉ የብዙሃን መገናኝ ኣጀንሲ ቦርድ ሰብሳቢ

2ኛ አቶ መሀመድ ያህያ- የክልሉ የብዙሃን መገናኝ ኣጀንሲ ቦርድ አባል

3ኛ አቶ ቶፊቅ መሀመድ-የክልሉ የብዙሃን መገናኝ ኣጀንሲ ቦርድ አባል እንዲሆኑ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።

በክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ አሪፍ መሀመድ አቅራቢነት

1ኛ አቶ ጅብሪል መሀመድ- የክልሉ ምክር ቤት የኢኮኖሚ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ

2ኛ ወ/ሮ ፊቲያ ሳኒ - በክልሉ ምክር ቤት የበጀትና ፋይናንስ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሰቢ ሆነው እንዲያገለግሉ ምክር ቤቱ በሙሉ ድምፅ ማፅደቁን የክልሉ ከሙዩኒኬሽን ቢሮ መረጃ አመልክቷል።


አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top