የማሌዢያ የንግድ ማኅበረሰብ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ያለውን የኢንቨስትመንት እድል እንዲጠቀሙ አበረታታለሁ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

5 Hrs Ago 30
የማሌዢያ የንግድ ማኅበረሰብ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ያለውን የኢንቨስትመንት እድል እንዲጠቀሙ አበረታታለሁ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የማሌዢያ የንግድ ማኅበረሰብ በፍጥነት በመስፋፋት ላይ ባለው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ያለውን የኢንቨስትመንት እድል እንዲጠቀሙ አበረታታለሁ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ኢብራሂም ብሎም የማሌዢያ ሕዝብ እና መንግሥት በቆይታችን ለሰጣችሁን ደማቅ አቀባበል እና ፍቅር እናመሰግናለን ብለዋል።

ትብብራችንን ትኩረታቸውን በግብርና፣ ማዕድን፣ ማኑፋክቸሪንግ እና ታዳሽ ኃይል ላይ ባደረጉ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ዘርፎች ብሎም ሰፊ አድማስ ባላቸው ሌሎች ቁልፍ ሥራዎች ላይ ለማጠናከር ተስማምተናል ሲሉም ገልፀዋል።


አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top