ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ንግግር ያደረጉበት ''የተጠናከረ የባለብዙወገን ግንኙነት ለሚዛናዊ የአለም ልማት እና ደኅንነት'' በሚል ጭብጥ የ16ኛው የብሪክስ ጉባኤ ዝግ ስብሰባ ዛሬ ጠዋት መካሄዱን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል።
ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2023 ወደብሪክስ እንዲቀላቀሉ ከተጋበዙት ሀገራት መካከል መሆኗ የሚታወቅ ሲሆን፤ ከጥር 2024 ጀምሮም የአባልነት እንቅስቃሴዋን በይፋ ጀምራለች።