የኢትዮጵያ ወንዶች እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ 2ኛ የምድብ ጨዋታውን ከቡርኪና ፋሶ አቻው ጋር ዛሬ ያደርጋል።
በካዛብላንካ ሞላይ ረሺድ ስታዲየም ልምምዱን ሲያከናውን የቆየው ብሔራዊ ቡድኑ፤ ለጨዋታው የመጨረሻ ልምምዱን ትናንት አድርጓል።
ሁለቱ ቡድኖች ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በአል-አብዲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ጃሚህ ለሚን ከጋምቢያ ጨዋታውን በዋና ዳኝነት እንደሚመሩት ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።