የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የ2016 የውድድር ዘመን ነገ በሚደረጉ ስድስት ጨዋታዎች እንደሚጀምር ከኢትዮያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ዘንድሮ በሁለት ምድቦች 28 ክለቦችን ተሳታፊ የሚያደርገው ውድድሩ፤ በሀዋሳ እና በአዲስ አበባ የሚከናወን ይሆናል።
በሁለቱም ምድቦች የውድድር አመራሮች እና ተሳታፊ ክለቦች የቅድመ ውድድር ስብሰባቸውን በዛሬው ዕለት አከናውነዋል።
የነገ መርሐ ግብሮች
ምድብ ሀ (አበበ ቢቂላ ስታዲየም)
04:00 - ጅማ አባ ጅፋር ከ ወልዲያ
08:00 - ነቀምቴ ከተማ ከ ኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከ
10:00 - ንብ ከ ቤንች ማጂ ቡና
ምድብ ለ (ሀዋሳ አርቲፊሻል ሜዳ)
04:00 - ቢሾፍቱ ከተማ ከ አዲስ ከተማ ክ/ከተማ
08:00 - ደሴ ከተማ ከ የካ ክ/ከተማ
10:00 ጋ- ሞ ጨንቻ ከ ካፋ ቡና