የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ ባከናወነው የምክክር ምዕራፍ ሂደት ውስጥ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
ለመሆኑ እነዚህ የባለድርሻ አካላት ወኪሎች የትኞቹን አካላት ወክለው ተሳተፉ?
- የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች
- ከየወረዳው የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን እንዲወክሉ የተመረጡ ተወካዮች
- የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች
- በአዲስ አበባ ከተማ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች
- የተቋማት እና ማህበራት ተወካዮች (በአዲስ አበባ ከተማ የተመዘገቡ)
- የሃይማኖት ተቋማት
- ሲቪል ማህበራት
- የአሰሪዎች ማህበራት
- የሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን
- የመምህራን ማህበር
- የአካል ጉዳተኞች ማህበራት
- የሙያ ማህበራት
- የቀድሞው ሠራዊት ማህበር (ተቀናሽ ሠራዊት ማህበር)
- የጋዜጠኞች ማህበር
- የዩኒቨርሲቲ መምህራን (የመንግሥት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት)
- የንግድ ማህበራት ምክር ቤት
- የሴቶች እና ወጣቶች ማህበራት
- የመንግሥት ተወካዮች (በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ያለው ሕግ አውጪ፣ ሕግ አስፈፃሚ እና ሕግ ተርጓሚ)
- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት
- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤት ዳኞች
- የአዲስ አበባ ከተማ ሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞች
- የአዲስ አበባ ከተማ ፓሊስ ኮሚሽን
- የተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተወካዮች
- በተለያዩ ዘርፎች በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያላቸው፣ አንቱታን ያተረፉ እና ተፅዕኖ መፍጠር የሚችሉ ግለሰቦች
ምንጭ፦ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
ኢትዮጵያ እየመከረች ነው!