የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ እንዲሁም የጅቡቲ ፓርላማ አፈ ጉባኤ ዲሌታ መሀመድ ዲሌታ እና የልዑካን ቡድናቸው በኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት ከአየር መንገዱ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል።
ከውይይቱ በተጨማሪ በቆይታቸው የአየር መንገዱን የተለያዩ የስራ ክፍሎች ተዘዋውረው መጎብኘታቸውን ከአየር መንገዱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።