የትግራይ ክልል በጦርነት የአካል ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች ለመርዳት በመቀሌ ያስገነባውን ማገገሚያ ማዕከል በዛሬው ዕለት አስመርቋል፡፡
ማዕከሉን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ እና የቀድሞ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል መርቀው መክፈታቸውን የትግራይ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ መረጃ ያመለክታል፡፡
የአካል ጉደኞች ማገገሚያ ማዕከል ተሰርቶ ለአገልግሎት እንዲበቃ ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋና ቀርቧል፡፡