የብላቴ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ማሰልጠኛ ማዕከል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ኮማንዶዎችን እያስመረቀ ነው

1 Yr Ago 2535
የብላቴ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ማሰልጠኛ ማዕከል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ኮማንዶዎችን እያስመረቀ ነው

የብላቴ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ማሰልጠኛ ማዕከል የተለያዩ አስቸጋሪ መሰናክሎችን ማለፍን እንዲሁም ፈጥኖ መድረስን ለሚጠይቁ ተልእኮዎች ጠንካራ ስልጠና የወሰዱ በሺዎች የሚቆጠሩ ኮማንዶዎችን ዛሬ እያስመረቀ ነው። 

የምርቃት በዓሉን በማስመልከት ሰልጣኞቹ ያገኙትን ክህሎት በትልቅ የአምሳለ-እውን ትርኢት አሳይተዋል። 

በመርሐግብሩም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሺዎች የሚቆጠሩ ታዳሚዎችን የማስተናገድ አቅም ኖሮት በማሰልጠኛ ማዕከሉ የተገነባውን አምፊቲአትር በይፋ ከፍተው በየአረንጓዴዐሻራ መርሃ ግብር ችግኞችን መትከላቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።


አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top