በሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክ የገበታ ጨው የሚያመርት ኩባንያ ወደ ስራ ለመግባት ስምምነት ፈፀመ

1 Yr Ago
በሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክ የገበታ ጨው የሚያመርት ኩባንያ ወደ ስራ ለመግባት ስምምነት ፈፀመ

ኤጂ ዋይ የተሰኘ የገበታ ጨው የሚያመርት ኩባንያ በሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክ በመግባት የገበታ ጨው ምርት ላይ ለመስራት ከኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር ስምምነት ፈፅሟል።

ኩባንያው 2000 ካሬ ሜትር የለማ መሬት በመረከብ እና የራሱን ማቀነባበሪያ በመገንባት ስራ የሚጀምር ሲሆን ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ የኢንቨስትመንት ካፒታልም ያስመዘገበ ነው ተብሏል። 

ኩባንያው በሙሉ አቅሙ ስራ ሲጀምር ከ350 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል እንደሚፈጥርም ተገልጿል።  

አሁን ላይ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክ በተለይም በዱቄት ወተት ምርትና ተያያዥ በሆኑ የአግሮ ፕሮሰሲንግ ዘርፎች ገብተው ኢንቨስት ለማድረግ ከፍተኛ ፍላጎት ያላቸው ባለሀብቶችን እያስተናገደ መሆኑን የኮርፖሬሽኑ መረጃ ያመለክታል።

ሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክ በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በ2 ሺ ሄክታር መሬት ላይ የተገነባ ሲሆን፤ 8 የማምረቻ ሼዶች የተገነቡለት እና ለጅቡቲ ወደብ ቅርበት ያለው ግዙፍ የኢንቨስትመንት ማዕከል ነው።


ተያያዥ ርዕሶች

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top