በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ የተመራ የክልል ርዕሳነ መስተዳደር ልዑካን መቐለ ገቡ

12 Mons Ago
በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ የተመራ የክልል ርዕሳነ መስተዳደር ልዑካን መቐለ ገቡ

በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ የተመራ የክልል ርዕሳነ መስተዳደር ልዑካን መቐለ ገብተዋል።

የሁሉም ክልል ርዕሰ መስተዳደሮቹ እና የአዲስ አበባና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች በመቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና የመቐለ ከተማ ነዎሪዎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የርዕሳነ መስተዳደሮቹ የመቐለ ጉዞ ለትግራይ ክልል አጋርነታቸውን ለማሳየት እና በመልሶ ግንባታ ሂደት የድርሻውን ለማበርከት ዓላማ ያደረገ ነው።
የክልል ርዕሳነ መስተዳደሮች፣ የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ ከንቲባዎች ወደ መቐለ ሲያቀኑ ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።
ከሰሞኑ በወዳጅነት አደባባይ በተካሄደው ‘ጦርነት ይብቃ፤ ሰላምን እናፅና’ በሚል መሪ ቃል በተካሄደ መርሐ ግብር ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች በመቐለ ጉብኝት እንደሚያደርጉ መናገራቸው ይታወሳል።
ሰለሞን አበጋዝ ከመቐለ

'


አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top