የቱርክ ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን ለኢትዮጵያ መንግሥት ምስጋና አቀረቡ

12 Mons Ago
የቱርክ ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን ለኢትዮጵያ መንግሥት ምስጋና አቀረቡ
የቱርክ ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን የኢትዮጵያ መንግሥት በአገሪቱ ተከስቶ በነበረው የርዕደ-መሬት አደጋ ወቅት ላደረገው አፋጣኝ የነፍስ አድን ድጋፍ እና ትብብር ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።
ፕሬዚዳንቱ በቱርክ ለኢትዮጵያ አምባሳደር አደም መሐመድ እና ለኢትዮጵያ የነፍስ አድን ቡድን መሪ ሌ/ጄኔራል ደስታ አቢቼ የሜዳሊያ እና የምስጋና ምስክር ወረቀት አበርክተዋል።
ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን በርዕደ-መሬት አደጋ ወቅት ድጋፍ ላደረጉ ሌሎች አገራትም የሜዳሊያ እና የምስጋና ምስክር ወረቀት ማበርከታቸውን በቱርክ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ገልጿል።

ተያያዥ ርዕሶች

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top