የዜጎችን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በተሟላ መንገድ ለመተግበር የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ የማይተካ ሚና አለው፡- አፈ-ጉባኤ ታገሠ ጫፎ

13 Days Ago
የዜጎችን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በተሟላ መንገድ ለመተግበር የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ የማይተካ ሚና አለው፡- አፈ-ጉባኤ ታገሠ ጫፎ
የዜጎችን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በተሟላ መንገድ ለመተግበር የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ የማይተካ ሚና እንዳለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሠ ጫፎ ገለጹ።
 
አፈ-ጉባኤው ይህንን ያሉት፤በፍትሕ ሚኒስቴር አዘጋጅነት በፌዴራል አስተዳደር ሥነ-ሥርዓት አዋጅና በሽግግር ፍትሕ ፓሊሲ በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ነው።
 
አስተዳደራዊ ፍትሕ የማኅበራዊ ፍትሕ የማዕዘን ድንጋይ ነውም ሲሉ አፈ-ጉባኤው ገልጸዋል።
 
የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ባማከለ መንገድ የተዘጋጀ እና በመላ ሀገሪቱ ግብዓት ተሰብስቦበት የተዘጋጀ ፓሊሲ ስለመሆኑ ተናግረዋል።
 
የፍትሕ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) የምክክር መድረኩን አላማ ካስተዋወቁ በኋላ፤ አፈ -ጉባኤ ታገሠ ጫፎ በፖሊሲውና ሥነ-ስርዓት አዋጁ የተዘጋጀውን የምክክር መድረክ በይፋ አስጀምረዋል።
 
በውይይት መድረኩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትን ጨምሮ በርካታ ባለድርሻ አካላት መሳተፋቸውን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top