ክለቦች የምዕተ ዓመት የዋንጫ ረሀባቸውን ያስታገሱበት (2024/25)

5 Days Ago 1245
ክለቦች የምዕተ ዓመት የዋንጫ ረሀባቸውን ያስታገሱበት (2024/25)

1. ክሪስታል ፓላስ - በ120 ዓመት የክለቡ ታሪክ ማንችስተር ሲቲን በማሸነፍ ለመጀመርያ ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን ያነሳበት።

ንስሮቹ ከአሁን በፊት ሁለት ጊዜ በኤፍ ኤ ዋንጫ ለፍጻሜ ቢደርሱም በማንችስተር ዩናይትድ ተሸንፈው ክብሩን ማጣታቸው ይታወሳል።

2. ጎ ኤሄድ ኤግልስ - በኤርዲቪዜው የሚሳተፈው ክለብ የደች ዋንጫን በታሪኩ ለመጀመርያ ጊዜ ሲያነሳ ዘንድሮ ከ 93 ዓመት በኋላ ከዋንጫ ጋር የተገናኝበት ሆኗል።

3. ኒውካስል ዩናይትድ - ከተመሰረተ 133 ዓመት የሆነው ኒውካስትል የእንግሊዝ ሊግ ካፕን ለመጀመርያ ጊዜ ያነሳበት ዓመት ሆኗል።ክለቡ ከዋንጫ ጋር ሲገናኝ ደግሞ ከ70 ዓመት በኋላ ነው።

4. ቦሎኛ - በጣልያን ዋንጫ ፍጻሜ ኤሲ ሚላንን በማሸነፍ ከ51 ዓመት በኋላ ከዋንጫ ጋር የተገናኝበት ነው።

በቀጣይ ሁለት ሳምንት ውስጥ መልስ ሊያገኙ የሚችሉ የረጅም ዓመታት የዋንጫ ጥያቄዎች

• ፒ ኤስ ጂ - በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ለፍጻሜ የደረሰው የፈረንሳዩ ሀብታም ክለብ ኢንተር ሚላን ማሸነፍ ከቻለ ለመጀመርያ ጊዜ የአህጉሩን ትልቁን ክብር የሚያሳካበት ይሆናል።

• ሪያል ቤቲስ - በአውሮፓ ኮንፍረንስ ሊግ ለፍጻሜ የደረሰው የስፔኑ ክለብ ቼልሲን ካሸነፍ ለመጀመርያ ጊዜ የአውሮፓ መድረክ ውድድር ላይ የነገሰበት ይሆናል።

• ቶተንሀም ሆትስፐርስ - በዩሮፓ ሊግ ፍጻሜ ከማንችስተር ዩናይትድ የሚገናኝበትን ፈተና በድል የሚወጣ ከሆነ የ40 ዓመታት የዩሮፓ ሊግ የዋንጫ ድርቁን ያስታግሳል።

• ሀሪ ኬን - በግል ደግሞ የ31 ዓመቱ እንግሊዛዊው ሃሪ ኬን ለመጀመርያ ጊዜ ከዋንጫ ጋር የተገናኝበት ዓመት ሆኖለታል።


አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top