የአማራ ክልል የባለድርሻ አካላት አጀንዳ ማሰባሰብ ምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው

4 Days Ago 262
የአማራ ክልል የባለድርሻ አካላት አጀንዳ ማሰባሰብ ምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው
በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአማራ ክልል ሁለተኛው ምዕራፍና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት የምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ምዕራፍ የማስጀመሪያ መድረክ በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።
 
በመድረኩ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከመንግስት አካላት፣ ከማኀበራት፣ ከተፅዕኖ ፈጣሪዎችና ተቋማት የተወከሉ ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
 
በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነሮች፣ ተሳታፊ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
 
ከመጋቢት 27 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ በሚገኘው የክልሉ የምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ምዕራፍ፣ የመጀመሪያውና 10 የማህበረሰብ ክፍሎችን የወከሉ ከ4 ሺህ 500 በላይ ተሳታፊዎች አጀንዳዎቻቸውን አሰባስበው በትናንትናው ዕለት ማጠናቀቃቸው ይታወሳል።
 
ዛሬ የጀመረው የባለድርሻ አካላት ምክክር እስከ ሚያዝያ 4 ቀን 2017 ዓ.ም ይቀጥላል።
 
በሳሙኤል ወርቃየሁ

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top