የነብዩላሂ ኢብራሂም የፈጣሪ ፍቅር፤ የኢስማኤል ታዛዥነት በአረፋ ተራራ ተፈትኖ አለፈ

7 Days Ago 324
የነብዩላሂ ኢብራሂም የፈጣሪ ፍቅር፤ የኢስማኤል ታዛዥነት በአረፋ ተራራ ተፈትኖ አለፈ
ነብዩላሂ ኢብራሂም ከአሏህ ነብያቶችና መልዕክተኞች መካከል አንዱ ናቸው። የትልቅ ስብዕና ባለቤት ሲሆኑ በሁሉም አጋጣሚ እና ሁኔታ አሏህን ፈሪም ነበሩ። ከጣኦት አምላኪ ቤተሰብ የወጡት ነብዩላሂ ኢብራሂም ገና በልጅነታቸው ነበር የሰው አለማስተዋል የተገነዘቡት።
የሚገርመው የኢብራሂም አባት ነበሩ ለከተማይቱ ህዝብ የተለያዩ ጣኦታትን እየሰሩ የሚሸጡላቸው። ነብዩላሂ ኢብራሂም በጣም ማሰላሰል እና ማገናዘብ ሲጀምሩ እንዴት አባቴ ከእንጨት እና ከድንጋይ እየጠረበ የሚሸጠውን ግዑዝ ነገር ሰው ያመልከዋል በማለት ትክክለኛውን አምላክ መፈለግ ጀመሩ። ትክክለኛውን አምላክ ፍለጋ ሲጀምሩ ጨረቃ፣ ፀሀይ፣ ኮከብ አምላክ ናቸው ብለው ሲወስኑ እነሱን የሚቆጣጠር አንድ አካል እንዳለ ተረዱ። ያ ጌታ ደሞ በአይን ሊታይ እንደማይችልም ተገንዝበው በዛ የፍጥረተ አለሙ ጌታው በሆነው አሏህ መሆኑን አመኑ።
ህዝቡንም ከዚህ አምልኮ ለማውጣት ሲሞክሩ ንጉሥ እና ህዝቡ ኢብራሂምን ለማቃጠል ተራራ የሚያክል አንጨት አቀጣጥለው ጣሏቸው አሳቸው በእሳቱ ላይ ለአርባ ቀን ቆይተው ሲወጡ ውበታቸው ሰባ እጥፍ ጨምሮ ነበር።
ነብዩላሂ ኢብራሂም ሚስታቸው ሳራ መሀን ስለነበረች ሳራ አገልጋያቸውን አግብተው ልጅ እንዲወልዱ ስትጠይቃቸው አይሆንም ቢሉም እሷ ግን አሳምነዋቸው ሀጃርን አገቡ።
ነብዩላሂ ኢብራሂም ሀጃር ከምትባል አጋራቸው የበኩር ልጃቸውን ኢስማኤልን ከወለዱ በኋላ፣ በቤታቸው እንዲቀመጡ በወቅቱ መካን የነበረችው ባለቤታቸው ሳራ ውስጧ አልፈቀደም ነበር፣ ታድያ በአንደኛው ቀን አላህ ለነቢዩላሂ ኢብራሂም ሀጀርና ኢስማኤልን ይዘው ወደ አረቢያ ምድር እንዲወጡ ነብዩ አዘዛቸው።
ነብዩላሂ ኢብራሂም የአላህን ቃል በመቀበል ምንም ምግብም ሆነ መጠጥ እንዲሁም መጠለያ ወደሌለው በረሀ አሁን ላይ መካ በመባል ወደምትታወቀ ቦታ ይዘዋቸው ይሄዳሉ እዛም እናት እና ልጁን ትተዋቸው ሄዱ።