የሰላም ተማፅኖ ድምጾች በአዲስ አበባ

1 Mon Ago 170
የሰላም ተማፅኖ ድምጾች በአዲስ አበባ
በአዲስ አበባ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች በትግራይ ያለው ሰላም ይፅና ሲሉ በሰላማዊ ሰልፍ ገልፀዋል::
 
"በፕሪቶርያ የተደረሰው የሰላም ስምምነት ተግባራዊ ይደረግ" ሲሉም ነው በአዲስ አባባ ስታዲየም ባደረጉት ሰላማዊ ሰልፍ የጠየቁት።
 
ከለሊት 11 ሰአት ጀምሮ ሰላማዊ ሰልፍ እያካሄዱ የሚገኙት የትግራይ ተወላጆች "የትግራይ ህዝብ ሰላም ይፈልጋል ፖለቲከኞች በሰከነ መንገድ አለመግባባታቸውን ይፍቱ" ሲሉ ተደምጠዋል።
 
የትግራይ ህዝብ ሰላም ይፈልጋል የትኛውንም ሰላሙን ለማፍረስ የሚደረግ ጥረት እንቃወማለን ሲሉም ገልፀዋል።
 
በመስከረም ቸርነት

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top