ሀሪ ኬን የመጀመሪያ ዋንጫውን አሳካ

62 Days Ago 555
ሀሪ ኬን የመጀመሪያ ዋንጫውን አሳካ
እንግሊዛዊው የፊት መስመር ተጫዎች ሀሪኬን በህይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በባየርን ሙኒክ ቤት ዋንጫ ማሳካት ችሏል።
 
በዛሬው የቦንደስሊጋ መርሀ ግብር ባየርሊቨርኩሰን ከፍራይበርግ 2 አቻ መለያየቱን ተከትሎ ባየርሙኒክ ለ34ኛ ጊዜ የቦንደስሊጋ ሻምፒዩን መሆኑን አረጋግጧል።
 
ከባየርሙኒክ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኘው ባየር ሊቨርኩሰን ከእንግዲህ ያሉትን 2 ጨዋታዎችን እንኳን ቢያሸንፍ እና ባየርሙኒክ ሁለቱንም ቢሸነፍ በመካከላቸው የ2 ነጥብ ልዩነት እያለ ባየርሙኒክ ያሸነፋል።
 
በመሆኑም ባየርሙኒክ 2 ጨዋታዎች እየቀሩት የ 2024/25 የቦንደስሊጋ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋግጧል።
 
ታዲያ ሀሪ ኬንም ከ16 አመታት ጥበቃ በኋላ ህልሙን አሳክቷል። እግር ኳስም በስተመጨረሻ ያከበራትን አክብራለች።
 
በሴራን ታደሰ

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top