ኢትዮ-ቴሌኮም የ5ኛው ትውልድ የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት በይፋ አስጀመረ

1 Yr Ago 286
ኢትዮ-ቴሌኮም የ5ኛው ትውልድ የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት በይፋ አስጀመረ

ኢትዮ-ቴሌኮም የ5ኛው ትውልድ (5G) የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት በዛሬው ዕለት በይፋ አስጀምሯል።

የ5G የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት በሰከንድ እስከ 10 ጊጋባይት የሚደርስ ከፍተኛ ፍጥነት እንዳለው ነው የተገለጸው።

አገልግሎቱን በይፋ ያስጀመሩት የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬሕይወት ታምሩ፣ ይህ አገልግሎት በአዲሱ ዓመት ዋዜማ መጀመሩ አዲስ ተስፋን የሚሰንቅ ነው ብለዋል።

የ5G ኔትወርኩ በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች መጀመሩም ተገልጿል። 


አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top