የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ለዘንድሮው ስድስቱ የጳጉሜን ቀናት የሰጠውን ስያሜ ይፋ አድርጓል።
በዚህም መሠረት፦
ጳጉሜን 1 - የአገልግሎት ቀን
ጳጉሜን 2 - የመሥዋዕት ቀን
ጳጉሜን 3 - የበጎነት ቀን
ጳጉሜን 4 - የአምራችነት ቀን
ጳጉሜን 5 - የትውልድ ቀን እና
ጳጉሜን 6 - የአብሮነት ቀን በሚል ተሰይመዋል።
ቀናቱ በመላ ሀገሪቱ በመንግሥት እና በግል ተቋማት ይከበራሉ።
የአብሮነት እሴትን ማጎልበት፣ የአገልጋይነትን ባህል ማሳደግ እና አንድነትን ማጠናከር ቀናቱን በማክበር ውስጥ የሚሳኩ ወይም የሚጠበቁ ግቦች ናቸው ተብሏል።
በንብረቴ ተሆነ