በደቡብ ክልል 2ኛው ምዕራፍ አረንጓዴ ዐሻራ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት በጌዲኦ ዞን ተጀመረ

1 Yr Ago 448
በደቡብ ክልል 2ኛው ምዕራፍ አረንጓዴ ዐሻራ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት በጌዲኦ ዞን ተጀመረ

በደቡብ ክልል ሁለተኛው ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት በጌዲኦ ዞን ተጀምሯል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ወናጎ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

አካባቢው በቡና፣ አቮካዶ፣ ማንጎና ሌሎች የፍራፍሬ ተክሎች በስፋት የሚታወቅ ሲሆን፤ በዘንድሮው አረንጓዴ ዐሻራ በጥምር ደን ልማት ላይ ትኩረት ይደረጋል ተብሏል።

በክልሉ በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው አሻራቸውን አኑረዋል።

በሮዛ መኮንን


አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top