አቶ ሰለሞን አረዳ የተመድ የግልግል ፍርድ ቤት የግማሽ ጊዜ ዳኛ በመሆን ቃለ መሐላ ፈፀሙ

5 Mons Ago
አቶ ሰለሞን አረዳ የተመድ የግልግል ፍርድ ቤት የግማሽ ጊዜ ዳኛ በመሆን ቃለ መሐላ ፈፀሙ

የቀድሞው የጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሰለሞን አረዳ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የግልግል ፍርድ ቤት የግማሽ ጊዜ ዳኛ በመሆን ቃለ መሐላ ፈፅመዋል።

አቶ ሰለሞን እ.ኤ.አ ኖቨምበር 15 ቀን 2022 በኒው ዮርክ በተካሄደው የተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባዔ የፍርድ ቤቱ የግማሽ ጊዜ ዳኛ ሆነው መሾማቸው ይታወሳል።

በዚሁ መሠረት አቶ ሰለሞን አዲሱን ሥራቸውን ከመጀመራቸው በፊት ባሳለፍነው ሳምንት በኒው ዮርክ በሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት ዋና መሥሪያ ቤት በመገኘት በሕጉ መሠረት የቃለ መሐላ ሥነ-ሥርዓት ፈጽመዋል።

ቃለ መሐላውን ያስፈጸሙት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ናቸው።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የግልግል ፍርድ ቤት በድርጅቱ ውስጥ የሚነሡ አስተዳደራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ዳኝነት የሚሰጥ ትልቅ የዳኝነት አካል ነው።


አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top