ከየካቲት 20-23፣2015 ድረስ በስፔን ባርሴሎና በተካሄደው የሞባይል ቴክኖሎጂ ኮንግረስ ላይ በሞባይል ትስስር ኢንዱስትሪው በዲጂታል ዓለም ውስጥ ለውጥ የሚያመጡ ስራዎች ቀርበውበታል።
በኮንግረሱ ላይ ተሳታፊ የነበረው ሁዋዌ ኩባንያ በኢንዱስትሪው ውስጥ ተፅዕኖ የሚፈጥሩ አዳዲስ ፈጠራዎችን ይዞ መቅረቡንም አስታውቋል።
በተለይም በክላውድ ቴክኖሎጂ የመረጃ መሰረተ ልማትን ለመገንባት የሚያስችል አዲስ የመረጃ ቋት ፣የዲጂታል ዓለሙ የክላውድ ቴክኖሎጂ አዲስ ገፀ በረከት ፣የዲጂታል አስታውሎት አገልግሎት እና ለዘመነው ዓለም የሚውል የመረጃ ቋት በመድረኩ ላይ ይፋ ከሆኑ የቴኬኖሎጂው ዘርፍ ግኝት ውስጥ ተጠቃሽ ናቸው።
ኩባንያው በ”ምርጥ የሞባይል ኔትዎርክ መሰረተ ልማት” እና በ”ምርጥ የሞባይል ቴክኖሎጂ ፈጠራ” በመድረኩ ላይ ተሸላሚ እንደነበርም ሁዋዌ ለኢቢሲሳይበር በላከው መግለጫ አስታውቋል።