የ3 ጊዜ የኦሎምፒክ እና የ5 ጊዜ የዓለም ሻምፒዮና አሸናፊዋ አትሌት ጥሩነሸ ዲባባ ከ10 ቀናት በኋላ በሚካሄደው 22ኛው የሂውስተን ግማሽ ማራቶን ላይ በመሮጥ ዳግም ወደ ውድድር ልትመለስ ነው::
አትሌት ጥሩነሽ በግማሽ ማራቶን 66 ደቂቃ ከ50 ሰከንድ የግሏ ፈጣን ሰዓት ያላት አትሌት ነች::
በሂውስተን ግማሽ ማራቶንም በርቀቱ 67 ደቂቃ ከ11 ሰከንድ ያላት አሜሪካዊቷ፣ ኤምሊ ሲሰን እና 66 ደቂቃ ከ47 ሰከንድ ያላት ኢትዮጵያዊቷ ህይወት ገ/ኪዳን የጥሩነሽ ተፎካካሪዎች ናቸው::