ምዕራባውያን በኢትዮጵያ ላይ በተናጠል ፖለቲካዊ ጫና በማሳደር እና ኢኮኖሚያዊ ማዕቀብ በመጣል የሚከተሉትን የተዛባ ፖሊሲ እንዲያቆሙ ሩስያ ጠየቀች።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ስለኢትዮጵያ በተደረገ ውይይት ላይ አስተያየት የሰጡት የሩስያ ምክትል ቋሚ ተወካይ አና ኤስቲግኒቫ የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት በኢትዮጵያ እና በቀጣናው ሰላም ለማምጣት የሚያደርጉትን የጋራ ጥረት እናበረታታለን ብለዋል።