• የፕሪቶሪያው ስምምነት ያጨናገፈባቸውን መንገድ አሁን በትግራይ የተፈጠረውን አጋጣሚ በመጠቀም የትግራይን ሕዝብ ለመጨፍጨፍ የተዘጋጁ ወገኖች አሉ
• የፌዴራል መንግሥት እንደዚህ ዓይነት ግጭት እንዳይከሰት በቂ ጥረት አድርጓል። ይህ ችግር እንዲከሰት ያደረጉት በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ ያሉ ጥቂት አካላት ናቸው።
• ማሕተም የሚነጥቀው ቡድን ምንም ዓይነት የሐሳብ ልዩነትን ለመቀበል ፍላጎት የሌለው ነው። ሥልጣን ያስገኝልኛል ያለውን የትኛውን ትርምስ ለመፍጠር የተዘጋጀ ኃይል አለ።
• ፌዴራል መንግሥት የሠራቸውን በጎ ነገሮች መጥቀስ በዚህ ቡድን ተወቃሽ እያደረገኝ ስለሆነ የፌዴራል መንግሥት ለመውቀስ እየተገደድኩ ነበር።
• የትግራይ ሕዝብ መሔድ ወደሚፈልገው ሳይሆን መስቀለኛ መንገድ ላይ ነው ያለው።
• የትግራይ ሕልውና ያስፈልጋል ብሎ የሚያምን አካል ሁሉ የሚቻለውን ማድረግ አለበት።
• የፕሪቶሪያ ስምምነት ዓላማ ተኩስ ማቆም ነው፤ የተስማማነውም አንድ መከላከያ ሠራዊት ብቻ እንዲኖር ነው።
• በክልሉ በርካታ መሠረተ-ልማቶች እንዲጠፉ ተደርገዋል።
• የኢኮኖሚ ዳግም ግንባታ ለማድረግ የሰላም ሁኔታዎችን መፍጠር አስፈላጊ ነው ብሎ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ያምናል።
• ለምሳሌ የ‘ዲዲአር’ (ተሃድሶ) ለመፈፀም የሚደረገው ጥረት በቂ አይደለም። አሁን ባለው ሁኔታ ምክንያት ሂደቱ በትክክል እየሄደ አይደለም።
• የተሃድሶ ሂደቱን ከማስቆም አንፃር ተጠያቂው እኛ ነን፤ የፌዴራል መንግሥቱ አይደለም። ለዚህ የፌዴራል መንግሥትን መውቀስ አልችልም።
• በተገኘው አጋጣሚ ወደ ድሮ ሥልጣኔ ልመለስ የሚለው ኃይል ትርምሱ በመቐለ ጭምር እንዲካሄድ እያደረገ ነው።
• የፌዴራሉን መንግሥት ተችቼ እንድጽፍ ተገድጄ ነበር ግን እኛው ራሳችን በፈጠርነው ትርምስ ነው ዲዲአሩ የተቋረጠው።
• የፌዴራል መንግሥትን ከሚፈለገው በላይ ተችቻለሁ፤ አምባሳደር በመጣ ቁጥር የፌዴራል መንግሥትን ወቅሻለሁ።
• ተፈናቃዮች እንዳይመለሱ ያደረግነው ራሳችን ነን፤ ምክንያቱም እነሱ ሲመለሱ አጀንዳ ይጠፋል በሚል።
• ለዚህ የፌዴራል መንግሥቱን ለምንድን ነው ሁሌም የምንወቅሰው? መወቀስ የለበትም።
• እኔ ባለሁበት ፓርቲ ውስጥ ባለው የተምታታ እሳቤ ከፌዴራል መንግሥት ጋር መሥራት በባንዳነት የሚያስፈርጅ ነው።
• ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ሔጄ የነጋዴን እና የገበሬን ጉዳይ ማስረዳት ሲገባኝ በባንዳነት እንዳልፈረጅ እየሰጋሁ ነው።
• ሥልጣንን ብቻ ዒላማ ያደረገው ቡድን ነው ይህን ነገር የሚፈጥረው፤ ሠራዊቱ ትርምስ አይፈጠረም።
• ካሜራ ፊት ባይሆንም በጎን በድብቅ ወደ ወንበሬ መልሰኝ በሚል ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሚጠይቁ አሉ።
• ሰላም ሲፈጠር እያዛለሁ፣ ፌዴራል መንግሥት ይይዘናል በሚል የሚፈሩ አሉ፤ እነዚህ ጥቂት ሰዎች ናቸው ሰላም እንዳይፈጠር የሚያደርጉት።
• ወጣቱ ወደ ሰላማዊ ሕይወት መመለስ ይፈልጋል። ይህንን ኃላፊነት ወደ ፌዴራል መንግሥቱ ብቻ መስጠት አያስፈልግም።