የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በወቅታዊ የክልሉ ሁኔታ ላይ ለተነሡላቸው ጥያቄዎች የሰጡት ምላሽ ዋና ዋና ነጥቦች

10 Days Ago 2232
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በወቅታዊ የክልሉ ሁኔታ ላይ ለተነሡላቸው ጥያቄዎች የሰጡት ምላሽ ዋና ዋና ነጥቦች

 • የፕሪቶሪያው ስምምነት ያጨናገፈባቸውን መንገድ አሁን በትግራይ የተፈጠረውን አጋጣሚ በመጠቀም የትግራይን ሕዝብ ለመጨፍጨፍ የተዘጋጁ ወገኖች አሉ

• የፌዴራል መንግሥት እንደዚህ ዓይነት ግጭት እንዳይከሰት በቂ ጥረት አድርጓል። ይህ ችግር እንዲከሰት ያደረጉት በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ ያሉ ጥቂት አካላት ናቸው።

• ማሕተም የሚነጥቀው ቡድን ምንም ዓይነት የሐሳብ ልዩነትን ለመቀበል ፍላጎት የሌለው ነው። ሥልጣን ያስገኝልኛል ያለውን የትኛውን ትርምስ ለመፍጠር የተዘጋጀ ኃይል አለ።

• ፌዴራል መንግሥት የሠራቸውን በጎ ነገሮች መጥቀስ በዚህ ቡድን ተወቃሽ እያደረገኝ ስለሆነ የፌዴራል መንግሥት ለመውቀስ እየተገደድኩ ነበር።

• የትግራይ ሕዝብ መሔድ ወደሚፈልገው ሳይሆን መስቀለኛ መንገድ ላይ ነው ያለው።

• የትግራይ ሕልውና ያስፈልጋል ብሎ የሚያምን አካል ሁሉ የሚቻለውን ማድረግ አለበት።

• የፕሪቶሪያ ስምምነት ዓላማ ተኩስ ማቆም ነው፤ የተስማማነውም አንድ መከላከያ ሠራዊት ብቻ እንዲኖር ነው።

• በክልሉ በርካታ መሠረተ-ልማቶች እንዲጠፉ ተደርገዋል።

• የኢኮኖሚ ዳግም ግንባታ ለማድረግ የሰላም ሁኔታዎችን መፍጠር አስፈላጊ ነው ብሎ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ያምናል።

• ለምሳሌ የ‘ዲዲአር’ (ተሃድሶ) ለመፈፀም የሚደረገው ጥረት በቂ አይደለም። አሁን ባለው ሁኔታ ምክንያት ሂደቱ በትክክል እየሄደ አይደለም።

• የተሃድሶ ሂደቱን ከማስቆም አንፃር ተጠያቂው እኛ ነን፤ የፌዴራል መንግሥቱ አይደለም። ለዚህ የፌዴራል መንግሥትን መውቀስ አልችልም።

• በተገኘው አጋጣሚ ወደ ድሮ ሥልጣኔ ልመለስ የሚለው ኃይል ትርምሱ በመቐለ ጭምር እንዲካሄድ እያደረገ ነው።

• የፌዴራሉን መንግሥት ተችቼ እንድጽፍ ተገድጄ ነበር ግን እኛው ራሳችን በፈጠርነው ትርምስ ነው ዲዲአሩ የተቋረጠው።

• የፌዴራል መንግሥትን ከሚፈለገው በላይ ተችቻለሁ፤ አምባሳደር በመጣ ቁጥር የፌዴራል መንግሥትን ወቅሻለሁ።

• ተፈናቃዮች እንዳይመለሱ ያደረግነው ራሳችን ነን፤ ምክንያቱም እነሱ ሲመለሱ አጀንዳ ይጠፋል በሚል።

• ለዚህ የፌዴራል መንግሥቱን ለምንድን ነው ሁሌም የምንወቅሰው? መወቀስ የለበትም።

• እኔ ባለሁበት ፓርቲ ውስጥ ባለው የተምታታ እሳቤ ከፌዴራል መንግሥት ጋር መሥራት በባንዳነት የሚያስፈርጅ ነው።

• ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ሔጄ የነጋዴን እና የገበሬን ጉዳይ ማስረዳት ሲገባኝ በባንዳነት እንዳልፈረጅ እየሰጋሁ ነው።

• ሥልጣንን ብቻ ዒላማ ያደረገው ቡድን ነው ይህን ነገር የሚፈጥረው፤ ሠራዊቱ ትርምስ አይፈጠረም።

• ካሜራ ፊት ባይሆንም በጎን በድብቅ ወደ ወንበሬ መልሰኝ በሚል ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሚጠይቁ አሉ።

• ሰላም ሲፈጠር እያዛለሁ፣ ፌዴራል መንግሥት ይይዘናል በሚል የሚፈሩ አሉ፤ እነዚህ ጥቂት ሰዎች ናቸው ሰላም እንዳይፈጠር የሚያደርጉት።

• ወጣቱ ወደ ሰላማዊ ሕይወት መመለስ ይፈልጋል። ይህንን ኃላፊነት ወደ ፌዴራል መንግሥቱ ብቻ መስጠት አያስፈልግም።


አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top