ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ኦክስጅን ማምረት ጀመረ

3 ወር በፊት
ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ኦክስጅን ማምረት ጀመረ

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሣይንስ ኮሌጅ ሥር የሚገኘው ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በውስጥ አቅም ኦክስጅን ማምረት መጀመሩ ተገልጿል፡፡

ሆስፒታሉ ሥራ በጀመረበት በትናንትናው ዕለት ብቻ 62 ኦክስጅን ማምረት መቻሉ ተመላክቷል፡፡

በቀጣይም ሆስፒታሉ የማምረት አቅሙን በማጠናከር የኦክስጂን ፍላጎቱን ሙሉ ለሙሉ በራስ አቅም ለመሸፈን እንደሚሠራ ተጠቅሷል፡፡

ሆስፒታሉ በቀን የሚያስፈልገውን ከ120 እስከ 150 ኦክሲጅን ሙሉ ለሙሉ በውስጥ አቅም ለመሸፈን ማቀዱን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሣይንስ ኮሌጅ መረጃ አመልክቷል፡፡


አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top