በገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የተመራው የኢትዮጵያ ልዑክ በቤጂንግ የሚገኘውን የአሊባባ ግሩፕ ዋና መስሪያ ቤትን ጎብኝቷል።
ልዑኩ የተቋሙን ታሪክ፣ የእድገት ሂደት እና የወደፊት ትንበያ የሚያስቃኘውን የኤግዚቢሽን አዳራሽ ተዘዋውሮ ተመልክቷል።
ልዑኩ ከጉብኝቱ በተጨማሪ በኢትዮጵያ እና በአሊባባ ግሩፕ መካከል በኢ-ኮመርስ እና በዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፎች ወደፊት ስለሚደረገው ትብብር
ከተቋሙ ምክትል ፕሬዝዳንት ሚስተር ሊዩ ናን እና ከሌሎች አመራሮች ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጉን በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ አመልክቷል።