የምንፈልጋትን ኢትዮጵያን ለመፍጠር በልጆች ላይ መሥራት እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ሳር ቤት አካባቢ እንደ አዲስ የተገነባ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራን ሥራ አስጀምረዋል።
ስመ ጥር ስፖርተኞችን ለመፍጠር በስፖርት ማዘውተሪያዎች ላይ መሥራት እንደሚገባም ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት “በአካል፣ በሥነ-ምግባር እና በሥነ-ልቡና የዳበረ ትውልድ ለመፍጠር የሚያግዘንን የስፖርት ማዘውተሪያ ገንብተናል።” ብለዋል።
የአካባቢው ተመሳሳይ የስፖርት ማዕከላትን እያስፋፋን እንቀጥላለን፤ ነገ የምንፈልጋትን ሀገር ለመገንባት በዛሬው ትውልድ ላይ መሥራት ይኖርብናል።” ሲሉም አክለዋል።