በአዲስ አበባ በትላንትናው ዕለት በጣለው ከባድ ዝናብ በንብረት እና በመሠረተ ልማት ላይ ጉዳት ደረሰ

1 Yr Ago
በአዲስ አበባ በትላንትናው ዕለት በጣለው ከባድ ዝናብ በንብረት እና በመሠረተ ልማት ላይ ጉዳት ደረሰ
በአዲስ አበባ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ልዩ ቦታው ፋና ወጊ በተባለ ቦታ በትላንትናው ዕለት (ሐምሌ 24 ቀን 2014 ዓ.ም) 9:00 ሰዓት ላይ በጣለው ከባድ ዝናብ በአካባቢው ነዋሪዎች ንብረት እና የኮብልስቶን ንጣፍ መንገድ እና የወንዝ ድጋፍ ግንባታ በመሳሰሉ መሠረት ልማቶች ላይ ጉዳት መድረሱን የከንቲባ ጽ/ቤት አስታወቀ።
በተጨማሪም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የወረዳ 9 እና የወረዳ 07 ነዋሪዎችን የሚያገናኝ ድልድይ ላይ ጉዳት መድረሱም ተገልጿል። በሌሎችም አከባቢዎች ለጎርፍ አደጋ ስጋት የሆኑ ቦታዎች ላይ ኅብረተሰቡ አስፈላጊውን ሁሉ ቅድመ ጥንቃቄ ያደርግ ዘንድ ጥሪ ቀርቧል።

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top